ዶ/ር ዳንኤል በቀለ፤ የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ) ዋና ኮሚሽነር የሥራ ጊዜ ገደባቸውን አጠናቅቀው ተሰናበቱ

የሥራ ጊዜያቸውን ያጠናቀቁትን የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን ዋና ኮሚሽነር ዶ/ር ዳንኤል በቀለን ያሰናበቱት፤ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አፈ ጉባዔ አቶ ታገሠ ጫፎ ናቸው።

Bekele.png

Dr Daniel Bekele, Chief Commissioner of the Ethiopian Human Rights Commission (L) and Tagesse Chafo, Speaker of the House of Peoples' Representatives (R). Credit: ENA

ዶ/ር ዳንኤል በቀለ፤ የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ) ዋና ኮሚሽነር ሆነው የተሾሙት ሰኔ 25 ቀን 2011 በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ይሁንታ ነው፡፡

የሕግ ባለሙያና የሰብ ዓዊ መብቶች ተሟጓች የነበሩት ዳንኤል በቀለ፤ ቀደም ሲልም የሰብዓዊ መብቶች ተመልካች ድርጅት የአፍሪካ ቅርንጫፍ ዳይሬክተር ሆነው ሠርተዋል።

በዓለም አቀፍ ሕግ ሶስተኛ ዲግሪያቸውን እንዲሁም በዓለም አቀፍ ሕግ ሰብዓዊ መብቶች ሁለተኛ ዲግሪያቸውን ያገኙት ከእንግሊዝ ኦክስፎርድ ዩኒቨርሲቲ ሲሆን፤ የመጀመሪያ ዲግሪያቸውን በማኅበራዊና የአካባቢያዊ ልማት የተቀበሉት ከአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ነው።

Share
Published 5 July 2024 6:38pm
Updated 5 July 2024 6:41pm
By Kassahun Seboqa Negewo
Source: SBS

Share this with family and friends