"የአድዋን ድል በዓል የማከብረው በአንድ ወቅት አንድ እና ታላቅ እንደነበርን ስለሚያስታውሰኝ ነው" አንዲት የአዲስ አበባ ነዋሪ

Adwa Menelik square.jpg

A banner was seen during the celebration of the 125th victory of Adwa at Menelik Square in Addis Ababa, Ethiopia, on March 2, 2021. - The Battle of Adwa was the climactic battle of the First Italo-Ethiopian War. The Ethiopian forces defeated the Italian invading force on March 1, 1896, near Adwa. The decisive victory thwarted the campaign of the Kingdom of Italy to expand its colonial empire in the Horn of Africa. Credit: AMANUEL SILESHI/AFP via Getty Images

128ኛውን የአድዋ ድል በዓል አከባበር አስመልክቶ ከአዲስ አበባ ነዋሪዎች አንደበት የተደመጡ አተያዮች።


የአድዋ ድል በአዲስ አበባ ነዋሪዎች አንደበት
ሌሎች አገራት የሚያከብሩት ከቅኝ ግዛት ነፃ የወጡበትን ቀን ነው፤ እና የምናከብረው የአድዋ በዓል የድል ቀን ነው።
አድዋ ለእኔ አገር ነው፤ ባለ አገር መሆን ማለት ነው።
የአድዋን ድል በየዓመቱ ሳይሆን በየቀኑ ነው የማስበው። ለእዚህች ዋጋ የተከፈለላት አገር ምን አደርጋለሁ ብዬ በየቀኑ ራሴን እጠይቃለሁ። እንደዚያ ነው የአድዋ ድልን የማከብረው።
የአድዋን በዓል በጣም ልጅ ሆኜ አክብሬያለሁ። ጊዮርጊስ አጥር ላይ ተንጠልጥዬ ጀግኖችን አይቻለሁ።
128ኛው የአድዋ ድል እንደምን ሊከበር ይገባል?
የአድዋ ድል በዓል ሲከበር የማኅበረሰብ አገልግሎት በመስጠት ቢከበር፤ እርዳታ ቢሰጥ ይጠቅማል። ጀግኖቻችን ደማቸውን ከፍለዋል፤ እኛ ገንዘባችንን ከፍለን ሕዝባችንን ልንታደግ ይገባል።

የአድዋ ድል በእኛ የልጅ ልጆቻቸው መከበር ያለበት በአንድነት ነው።
መስቀል አደባባይ ላይ ትርዒቶች ቢካሔዱ ደስ ይለኛል።
ኢትዮጵያዊነትን በማሰብ አሁን ያሉብንን የመከፋፈልና የመራራቅ ችግሮች አሸንፈን በአንድነት መጥተን ቢከበር ደስ ይለኛል። አዲሱን የአድዋ ሙዚየም ፕሮጄክት ዕውን ላደረጉት ሁሉ ምስጋናዬን አቀርባለሁ።

Share